የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጽ/ቤት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሚገኙ የአእምሯዊ ንብረት ሃብቶ …

የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጽ/ቤት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጋር በመተባበር ለቤተክርስቲያኗ ቤተክህነት የአስተዳደር መምሪያ ኃላፊዎችና ልዩ ኮሚቴ አባላት በአእምሯዊ ንብረት ጽንስ ሃሳብና የጥበቃ ስርዓት ዙሪያ የካቲት 12 ቀን 2011 ዓ.ም በቤተክህነቱ ቅፅር ግቢ ሥልጠና ሰጠ፡፡

የቤተክህነቱ ልዩ ኮሚቴ ተወካዮች ቤተክርስቲያኗ ያሏትን የአእምሯዊ ንብረት ሃብቶች ለማስመዝገብና ለማስጠበቅ ከጽ/ቤቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ተከትሎ ሥልጠናው የተዘጋጀ ሲሆን የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ፣ የማህበረሰብ እውቀቶችና የትውፊት ሃብቶች ጥበቃ እንዲሁም የፓተንት መብት ጥበቃ ሥርዓቶችን አስመልክቶ በባለሙያዎች ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡

ቤተክርስቲያኗ ያሏትን ዘርፈ ብዙ ሃብቶች በመደበኛ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ ህጎች እና በሌሎች አግባቦች ማስጠበቅ በምትችልባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት ተካሄዷል፡፡

Share this
CONTACT US

Email : info@eipa.gov.et
Address:

+251 115 52 80 00
+251 115 52 72 02
Fax:-  +251 115 52 92 99
Po.Box:- 25322/1000

USFULL LINKS