የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዘርፉ በአእምሯዊ ንብረት መብቶች መደገፍ እንደሚገባው ተገለጸ

ኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣንን ጨምሮ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር “የዳያስፖራው ሚና በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን” በሚል መሪ ሃሳብ ጥር 5/2014 ዓ.ም ምክክር አካሄደ፡፡

ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዘርፍ የምታደርገውን ርብርብ የአእምሯዊ ንብረት መብቶች ተደግፎ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ጉልህ ድርሻ እንዲያበረክት የዲያስፖራው አባላት ድጋፍ አዎንታዊ ተጽእኖ እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡

በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ምርምር ዘርፎች ላይ የተሰማሩ የግልና የመንግስት ተቋማት አዳዲስ ግኝቶቻቸውንና የምርምር ውጤቶቻቸውን ወደ ኢንቨስትመንት አማራጮች ለማሸጋገር ከዳያስፖራው ጋር በትብብር መስራት የሚያስችል ፎረም መቋቋሙ ተገልጿል፡፡  

CONTACT US

Email : info@eipa.gov.et
Address:

+251 115 52 80 00
+251 115 52 72 02
Fax:-  +251 115 52 92 99
Po.Box:- 25322/1000

USFULL LINKS