ኢትዮጵያ የዓለም አእምሯዊ ንብረት ድርጅት በሚያዘጋጀው የሃገራት የኢኖቭሽን መለኪያ ከፍተኛ እመርታ ማሳየቷ ተመላከተ

ኢትዮጵያ በ2022ቱ የዓለም የአእምሯዊ ንብረት ድርጅት የሃገራት የኢኖቬሽን ደረጃ መለኪያ በ2020 ከነበረችበት የ127ኛ ደረጃ እና በ2021 ከነበረችበት የ126ኛ ደረጃ አስራ አንድ ደረጃዎችን በማሻሻል 117ኛ ደረጃን መያዝ ችላለች፡፡

ይህ መረጃ እንደሚያሳየው ኢትዮጵያ የሃገራትን የኢኮኖሚ ደረጃ መሰረት በማድረግ በተደረገ ትንተና ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው 12 ሃገራት መካከል የ3ኛ ደረጃ ይዛ ትገኛለች፡፡ 80 የመለኪያ መስፈርቶችን በመጠቀም የሃገራቱን የኢኖቬሽን ደረጃ የሚለካው ይህ መረጃ ከሳህራ በታች ካሉ 46 ሃገራት መካከል ኢትዮጵያ 14ኛ ደረጃን የያዘች ሲሆን ደረጃቸውን ካሻሻሉ 16 ሃገራት መካከል ኢትዮጵያ ከፍተኛ እመርታን ከስመዘገቡት አንዷ መሆኗን ጠቁሟል፡፡

ይኸው መረጃ ስዊዘርላንድን፣ አሜሪካን እና ስዊድንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ የያዙ ሲሆን ቻይና 11ኛ፣ እስራኤል 16ኛ እንዲሁም ህንድ የ40ኛ ደረጃ መያዛቸውን አስቀምጧል፡፡    

Share this
CONTACT US

Email : info@eipa.gov.et
Address:

+251 115 52 80 00
+251 115 52 72 02
Fax:-  +251 115 52 92 99
Po.Box:- 25322/1000

USFULL LINKS